Yehonegn Tila
Daniel Amdemichael
4:51አዝ: - ከሁሉም ፡ የሚበልጥብኝ ፡ በማንም ፡ የማለውጠው አንበሳው ፡ የጀግኖች ፡ ጀግና ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው (፪x) ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው ፍቅሩ ፡ ግሩም ፡ እጁ ፡ ሰፊ ፡ ነው ምንተስኖት ፡ ምን ፡ ያሳጣኛል ቸርነቱን ፡ አብዝቶልኛል (፪x) ያለፈው ፡ ታሪኬ ፡ አፍ ፡ አለው ፡ ያወራል የጌታን ፡ ምህረት ፡ ፍቅር ፡ ይዘክራል ያልተደረገልኝ ፡ ያልሆነ ፡ ምን ፡ አለ የአምላኬ ፡ ምህረት ፡ በእኔ ፡ ገነነ ያልተደረገልኝ ፡ ያልሆነ ፡ ምን ፡ አለ የጌታ ፡ ምህረት ፡ በእኔ ፡ ገነነ ይረዳል ፡ እኮ ፡ ከማንም ፡ በላይ ተገርሜያለሁ ፡ ተአምራቱን ፡ ሳይ ምስክሩ፡ ነኝ ፡ ሕያው ፡ ምልክቱ ማዳኑን ፡ ያየሁ ፡ ሁሉን ፡ ቻይነቱን (፪x) አዝ: - ከሁሉም ፡ የሚበልጥብኝ ፡ በማንም ፡ የማለውጠው አንበሳው ፡ የጀግኖች ፡ ጀግና ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው (፪x) ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው ፍቅሩ ፡ ግሩም ፡ እጁ ፡ ሰፊ ፡ ነው ምንተስኖት ፡ ምን ፡ ያሳጣኛል ቸርነቱን ፡ አብዝቶልኛል (፪x) ምህረቱን ፡ እውነቱን ፡ ፍቅሩን ፡ አስብና የከበረ ፡ ስሙን ፡ አሞጋግስና ሳመልከው ፡ ሳከብረው ፡ እጅግ ፡ ደስ ፡ ይለኛል ልዘምር ፡ ድንቁን ፡ በምክሩ ፡ ስቦኛል አምላክ ፡ ለክብሩ ፡ በስሜ ፡ ጠርቶኛል ያስደስተኛል ፡ የጌታ ፡ መሆኔ ምህረት ፡ አገኘሁ ፡ ዳንኩኝ ፡ ከኩነኔ (፪x) አዝ: - ከሁሉም ፡ የሚበልጥብኝ ፡ በማንም ፡ የማለውጠው አንበሳው ፡ የጀግኖች ፡ ጀግና ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው (፪x) ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው ፍቅሩ ፡ ግሩም ፡ እጁ ፡ ሰፊ ፡ ነው ምንተስኖት ፡ ምን ፡ ያሳጣኛል ቸርነቱን ፡ አብዝቶልኛል (፪x)