Wsejat
Madingo Afework
5:12ተንገበገበልሽ አረረልሽ ሆዴ አትራቂኝ በኔ ሞት አይብዛ መንደዴ ያስታርቀን መውደዴ ልመናዬን ስሚኝ ይቅርታሽ ይድረሰኝ ጥፋቴን ለመርሳት እኔ አቅም አነሰኝ ልቤ እየወቀሰኝ ከትዝታሽ ንዳድ አልዳነም አንጀቴ አንቺን ካጣሁ ወዲህ ተጨንቋል ስሜቴ አልበላም አልጠጣም እምቢ እያለኝ ሆዴ ለይግባኝ ሳይታይ ሊቀር ነው ወይ ፍርዴ የእድሜዬን ጧት ማታ በትካዜ ገፋሁ አጣሁት ሰላሜን አንቺን ስላስከፋሁ ያለውን ችያለሁ መጪው ካልከበደኝ ፀልይልኝ ፍቅርሽ እንዳያሳብደኝ ላንቺ ይብላኝ እንጂ አልል አልተመቸኝ ላንቺ ይብላኝ እንጂ አልል አልተመቸኝ እወዳታለሁ ማለት አይሰለቸኝ እወዳታለሁ ማለት አይሰለቸኝ ተራዬን ብነሳ ልበር እንደገዴ ብመርጠው መራቁን በልጥራኝ መንገዴ ስትሄጂ ቢከፋኝ ስሞታ አላሰማ ተለየሽኝ ብዬ ዛሬ አንቺን አላማ ክፉሽን አውርቼ አልኖርም ሲቆጨኝ ቅናት ነው ጠላቴ እኔ የሚያነጫንጨኝ ዳር እስከ ዳር ብዞር ልክሽን አላገኝ ልርሳሽ ብል መንፈሴ ሰውም አያረገኝ እንባዬን ባፈሰው አፍ ላይ ደቀኑበት የኔ ቃላት ናቸው እኔን የቀኑበት አይኔን እየረሳሁ በዛፍ በቅጠሉ ተብሰልሳይ አርጎኛል ካንቺ መነጠሉ ትካዜን አጥምደው ምንም ቢፈዙበት ያዩበታል እንጂ ወፍን አይዙበት እባክሽ እባክሽ ታረቂኝ ተይ አታስጨንቂኝ እባክሽ እባክሽ ታረቂኝ ተይ አታስጨንቂኝ ልቦናሽ ከኔ አካል ሊርቅ መወሰኑ ጠፍቶብሽ ይሆን ወይ የመቻል ወሰኑ አንድም ፀፅቶኛል ለሱ በይኝ ይቅር አይለምደውም ጥፋት ሰው ሲቀጣው ፍቅር ልቦናሽ ከኔ አካል ሊርቅ መወሰኑ ጠፍቶብሽ ይሆን ወይ የመቻል ወሰኑ አንድም ፀፅቶኛል ለሱ በይኝ ይቅር አይለምደውም ጥፋት ሰው ሲቀጣው ፍቅር እሄሄሄ እሄሄሄ ነይ ምነው በትዝታ ሁሌ እንደምመኝሽ ከጉጉቴ መረብ ተቀምጠሽ ባገኝሽ እኔ አዳኝ አይደለሁ አላልም በጫካ ምንሽሬ እንባ ነው ምንም ባይሳካ ብዙ ማልቀስ በአዳም ባይለመድ እንኳን ባንቺ ሀዘን ልቤ ላይ አስጥያለሁ ድንኳን ብትሰባብረኝም ምድር ለአራት ታጥፋ አብረን እንኑርና እስኪ አብሬሽ ልጥፋ ቀራኒዮም ይስማ ጎሎጎታም ይወቅ አይረዳን ምረቱ እኛ ሳንታረቅ ባይፃፍም ሰዓት ላለም መጨረሻ ቀን ማጣት ምፃት ነው ላንቺ መመለሻ እባክሽ እባክሽ ታረቂኝ ተይ አታስጨንቂኝ እባክሽ እባክሽ ታረቂኝ ተይ አታስጨንቂኝ