Endet Tedrgo Yeweral
Temesgen Markos
5:46እንደልቡ ሃሳብህን ልክ እንደ ፈቃዱ ለእርሱ የተለዩለት ለአንዱ ለሰገዱ መስለውት በመኖር ጌታን ላስከበሩ ዋጋ አለ ከእርሱ ዘንድ ሲመጣ በክብሩ ስለዚህ ወገኔ አስብ አስተውል በዚህች ዓለም ነገር እንዳትታለል አንድ ቀን ወደላይ በክብር ከእርሱ ጋር ስትሄድ በደመና ወደ አምላክ እግዚአብሔር የዘለዓለም ደስታ የሁልጊዜ እረፍት ሃዘን በሌለበት ደስ የሚያሰኝ ገነት ትኖራለህ በዚያች ቅድስቲት ከተማ ስለዚህ ወገኔ ከእርሱ ጋር ተስማማ ኑርለት ኑርለት ለጌታ ኑርለት ኑር እንደሃሳቡ ኑርለት ኑር እንደፈቃዱ ያን ጊዜ ታያለህ እርሱ አንተን መውደዱ እንደፈቃድህ መኖርን መኖርን አስተምረኝ ለሃሳብህ መኖርን መኖርን አለማምደኝ ለፈቃድህ መኖርን መኖረን አስተምረኝ ለሃሳብህ መኖርን መኖርን አለማምደኝ ልኑር ልኑር እንደ ፈቃድህ ልኑር እንደ ሃሳብህ ልኑር ፀጋህ ይርዳኝ ጉልበት ስጠኝ እኔ አልችልም ባክህ አግዘኝ አውቀህ አገልግለህ አምላክህን በክብር ሚገባውን መጽዋት አቅርብ ከእግሩ ስር ከቶ እንዳትሰማ የጠላትን ወሬ ክብርህ ኢየሱስ ነው አስተውል ወገኔ ለአፍታ እንዳትዘነጋ የመቆምህን ሚስጥር ዛሬን የማየትህ በእርሱ ነው በእግዚአብሔር ክብርና ዝና ሃብት ስላለህ ሳይሆን ስለመረጠህ ሰው ስለለየህ አንተን ኑርለት ኑርለት ለጌታ ኑርለት ኑር እንደሃሳቡ ኑርለት ኑር እንደፈቃዱ ያን ጊዜ ታያለህ እርሱ አንተን መውደዱ እንደፈቃድህ መኖርን መኖርን አስተምረኝ ለሃሳብህ መኖርን መኖርን አለማምደኝ ለፈቃድህ መኖርን መኖረን አስተምረኝ ለሃሳብህ መኖርን መኖርን አለማምደኝ ልኑር ልኑር እንደ ፈቃድህ ልኑር እንደ ሃሳብህ ልኑር ፀጋህ ይርዳኝ ጉልበት ስጠኝ እኔ አልችልም