Setewed Bezu
Yohannes Girma
7:34አዝ፦ የልቤ ፡ ደስታ ፡ ጌታ የልቤ ፡ ደስታ ፡ የሱስ በገናዬን ፡ ልያዝ ፡ ልቀኝልህ ነፍሴ ፡ ውላ ፡ ታድራለች ፡ በስምህ (፪x) ምንም ፡ በሌለበት ፡ ማይነጥፍ ፡ ደስታ ብር ፡ ያልደጋገፈው ፡ የዚህ ፡ አለም ፡ ስጦታ ፊትን ፡ የሚያበራ ፡ ከላይ ፡ የሆነው ዘላቂው ፡ ደስታዬ ፡ ጌታ ፡ ባንተ ፡ እኮ ፡ ነው አዝ፦ የልቤ ፡ ደስታ ፡ ጌታ የልቤ ፡ ደስታ ፡ የሱስ በገናዬን ፡ ልያዝ ፡ ልቀኝልህ ነፍሴ ፡ ውላ ፡ ታድራለች ፡ በስምህ (፪x) አይኖቼን ፡ ወደ ፡ ተራሮች ፡ ባነሳ መመኪያን ፡ ለማግኘት ፡ ለእኔ ፡ የሚሳሳ ለአይን ፡ የሚሞላ ፡ ከቶ ፡ አንድም ፡ አላየሁ ይልቅ ፡ ባንተ ፡ ሆነ ፡ ልቤን ፡ ደስ ፡ የሚለው አዝ፦ የልቤ ፡ ደስታ ፡ ጌታ የልቤ ፡ ደስታ ፡ የሱስ በገናዬን ፡ ልያዝ ፡ ልቀኝልህ ነፍሴ ፡ ውላ ፡ ታድራለች ፡ በስምህ (፪x) በስደት ፡ ምድር ፡ ላይ ፡ በደረቅ ፡ በረሃ ለአይን ፡ ተስፋ ፡ ሳይኖር ፡ ለጥም ፡ የሚሆን ፡ ውሃ ዙሪያ ፡ ሲጨላልም ፡ መጽናናት ፡ ሲሳነኝ በእንግድነት ፡ ሀገር ፡ ስራህ ፡ መዝሙር ፡ ሆነኝ አዝ፦ የልቤ ፡ ደስታ ፡ ጌታ የልቤ ፡ ደስታ ፡ የሱስ በገናዬን ፡ ልያዝ ፡ ልቀኝልህ ነፍሴ ፡ ውላ ፡ ታድራለች ፡ በስምህ (፪x)