Mistren Yemigelts
Azeb Hailu
4:38ጽድቅን እንዲያወራ ምላሴ እንድትረካ እንድታርፍ ነፍሴ የዋጀኸኝ አምላኬ መድህኔ ከዚህች ዓለም አበሳ ኩነኔ እንዳይረክስ በከንቱ ከንፈሬ እንዳልጥለው ድንቁን ክብሬ ዘመኔን በእጆችህ ያዝክና አራመድከኝ በሕይወት ጐዳና ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ ከሃጥያት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ ከሃጥያት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ እንድረዳ ማዳንህን እንዳውቀው ልቦናዬን ወዳንተ የመለስከው እንዳያልፈኝ የሕይወቴ መና ሕሊናዬን ለቃልህ አቀናህ በረከሰው ዓለም የቀደስከኝ በጽድቅ መንገድ ላይ የመራኸኝ ከብዙዎች እኔ ተለይቼ ዘምራለሁ መቅደስህ ገብቼ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ ከሃጥያት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ ከሃጥያት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ አልመኝም ከእንግዲህ ወደ ውጪ ረክቻለሁ ጌታ አንተን መርጬ የዓለምን ከንቱነት ኮተቷን ንቄዋለሁ ከነማንነቷ ወስኛለሁ ልኖር አስከብሬህ ላፈራልህ ጣፋጭ መልካም ፍሬ ደስ እንዲልህ ሁሌ በእኔ ጌታ እገዛለሁ ፈቅጄ በደስታ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ ከሃጥያት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ ከሃጥያት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ