Alresawem
Daniel Amdemichael
4:41በሠማይ ዙፋኑ በመቅደሱ ያለው የፍጥረት ፈጣሪ እግዚአብሔር ድንቅ ነው ዓይኑ እንዳየ አይፈርድ ጆሮው እንደሰማ በምክሩ ትክክል ታማኝ ነው እርሱማ ልብን ኩላሊትን የሚመረምረው እንደሰው ያይደለ እግዚአብሔር ጻዲቅ ነው የሚያድን ነው ደግሞም የሚራራ አቤቱ ማረኝ ላለ ወደ እርሱ ለተጠጋ ውድ ልጁ በመረቀልን በር ወደ እርሱ መግባት አለ አሄ ታላቅ ስሙ ይክበር በምክሩ ጠቢብ ፍቅሩ የላቀ በልጆቹ ላይ ግርማው የደመቀ ምሥጋና ሞላ በማደሪያው ላይ በመንጋው መልካም ማዳኑን ሲታይ በሠማይ ዙፋኑ በመቅደሱ ያለው የፍጥረት ፈጣሪ እግዚአብሔር ድንቅ ነው ዓይኑ እንዳየ አይፈርድ ጆሮው እንደሰማ በምክሩ ትክክል ታማኝ ነው እርሱማ ልብን ኩላሊትን የሚመረምረው እንደሰው ያይደለ እግዚአብሔር ጻዲቅ ነው ታናሹን ሰው ለክብር የሚያበቃው የዳዊት የሙሴ አምላክ አሄ ለትሁቱ ጠበቃ የወህኒውን መዝጊያ የሚሰብር ለባሪያዎቹ ፈራጅ የሚሆን ሞገስ ክብር አቢት እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው በመልካም ዜማ እስቲ እናምልከው ክብሩ ይታወጅ በቤቱ መድረክ የዘለዓለሙ አምላክ ይባረክ በሠማይ ዙፋኑ በመቅደሱ ያለው የፍጥረት ፈጣሪ እግዚአብሔር ድንቅ ነው ዓይኑ እንዳየ አይፈርድ ጆሮው እንደሰማ በምክሩ ትክክል ታማኝ ነው እርሱማ ልብን ኩላሊትንየሚመረምረው እንደሰው ያይደለ እግዚአብሔር ጻዲቅ ነው ተራሮችን ከላይ የሚያጠጣ ለጻድቅ ለሃጥኡ አሄ ፀሐይን የሚያወጣ ደረቁን ምድር የሚያለመልመው ለታናሹ ሰው ብርታት እህ ሞገስ የሚሰጠው ምሥጋናን ያምጡ ለእርሱ ያደሩ በመንፈሱ ኃይል እየዘመሩ የቤቱ ካህናት ምስክሮቹ ስሙን ያክብሩ ታማኝ ባሮቹ በሠማይ ዙፋኑ በመቅደሱ ያለው የፍጥረት ፈጣሪ እግዚአብሔር ድንቅ ነው