Fikerehen
Daniel Amdemichael
6:53አዝ: - እርሱ ፡ ነው ፡ የደሃ ፡ ደግ ፡ ወዳጅ ፡ የባልቴቶች ፡ ዳኛ ድሃውን ፡ ምግቡን ፡ የሚያጐርሰው ፡ ጾሙን ፡ እንዳይተኛ የተጣለውን ፡ አይቶ ፡ የማያልፍ ፡ ከትቢያ ፡ ሚያነሳው እሩህሩህ ፡ ነው ፡ ጌታ ወዳጅ ፡ ዘመድ ፡ ገፍቶ ፡ ላራቀው ኢየሱስ ፡ ይደርስለታል ፡ አምላኬ ፡ ይደርስለታል ልቡን ፡ ሃዘን ፡ በጣም ፡ ለጐዳው መጽናናት ፡ ይሆንለታል (፪x) ማረፊያ ፡ ነው ፡ ለተጣለው ፡ ሰው አይተናል ፡ እንባውን ፡ ሲያብሰው (፪x) ከቅዱሳን ፡ መሃል ፡ ሲያቆመው ሲያከብረው ፡ ሞገስ ፡ ሲሆነው (፪x) ድንቅ ፡ ፍቅሩን ፡ አይቻለሁ ፡ መጠጊያ ፡ ሆኖኝ ፡ መድህኔ ወጀቡ ፡ እንዳያንገላታኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ሲቆም ፡ ከጐኔ ባወራው ፡ ቃላት ፡ ያጥረኛል ፡ ብቆጥረው ፡ የእርሱን ፡ ውለታ እንዲያው ፡ ላመስግነው ፡ እንጂ ፡ በጠዋት ፡ ደግሞም ፡ በማታ አዝ: - እርሱ ፡ ነው ፡ የደሃ ፡ ደግ ፡ ወዳጅ ፡ የባልቴቶች ፡ ዳኛ ድሃውን ፡ ምግቡን ፡ የሚያጐርሰው ፡ ጾሙን ፡ እንዳይተኛ የተጣለውን ፡ አይቶ ፡ የማያልፍ ፡ ከትቢያ ፡ ሚያነሳው እሩህሩህ ፡ ነው ፡ ጌታ ቸርነቱን ፡ ያውራ ፡ የቀመሰው ፡ ይዘምር ፡ እንደኔ ፡ ያለው (፪x) ማቁን ፡ ቀዶ ፡ ደስታ ፡ ያስታጠቀው ፡ ምህረቱ ፡ ሰው ፡ ያደረገው (፪x) ምንም ፡ የለም ፡ የኔ ፡ የምለው ፡ አንድ ፡ ሁለት ፡ ብዬ ፡ ምቆጥረው (፪x) ጽድቄም ፡ ቅድሳዬ ፡ እርሱ ፡ ነው ፡ በመስቀል ፡ ለእኔ ፡ የሞተው በመስቀል ፡ ሁሉን ፡ የሰራው ሁሉም ፡ ነገር ፡ ተፈጸመ ፡ ተፈጸመ ፡ ያለ ፡ ለታ አሮጌው ፡ ማንነት ፡ አልፎ ፡ በአዲሱ ፡ ሕይወት ፡ ተተካ አፋቸው ፡ ምሥጋና ፡ ሰማ ፡ ኢሄ ፡ ሚስጥር ፡ የገባቸው በትንሳኤው ፡ የለበሱት ፡ ኢየሱስ ፡ ሁኖ ፡ ኑሯቸው ለእኔስ ፡ ብርሃን ፡ በርታልኛለች ፡ ከሰማይ ፡ ድምቅ ፡ እያለች (፪x) ጨለማውን ፡ እየገፈፈች ፡ የጌታን ፡ ጽድቅ ፡ እያሳየች ፤ የአምላኬን ፡ ጽድቅ ፡ እያሳየች የመስቀሉ ፡ ስራ ፡ ስገለጥ ፡ በሕይወቴ ፡ እውነት ፡ ሲበራ አስታረቀኝ ፡ ከአምላኬ ፡ ጋራ ፡ ይዘመር ፡ ይሄስ ፡ ይወራ (፪x) ምሰጠው ፡ አንዳች ፡ የእልኝም ፡ ማን ፡ ልበለው ፡ መድሃኒቴን ምሥጋናን ፡ ሰላም ፡ ደስታን ፡ እርካታን ፡ ሞልቷል ፡ ሕይወቴን ልቀኝለት ፡ አዲስ ፡ ቅኔን ፡ ይበልጣል ፡ እርሱ ፡ የፈቀደው ለሥሙ ፡ ምሥጋና ፡ ይሁን ፡ ለኢየሱስ ፡ ጌታ ፡ ለሆነው አዝ: - እርሱ ፡ ነው ፡ የደሃ ፡ ደግ ፡ ወዳጅ ፡ የባልቴቶች ፡ ዳኛ ድሃውን ፡ ምግቡን ፡ የሚያጐርሰው ፡ ጾሙን ፡ እንዳይተኛ የተጣለውን ፡ አይቶ ፡ የማያልፍ ፡ ከትቢያ ፡ ሚያነሳው እሩህሩህ ፡ ነው ፡ ጌታ