Yigeza Gulbete
Meskerem Getu
4:44አንተን ተስፋ አድርጌ መጥቼ ነበረ ፀሎቴን ሰምተሃል ስለቴ ሠመረ ፀሎትን ትሰማለህ እንባንም ታብሳለህ ለሚጠሩህ ቅርብ ነህ ደጅህን ትከፍታለህ ኡ አንዳንድ ጊዜ እታወካለሁ የሚነፍሰው ነፋስ ታንኳየን ሲንጠው ኡ መርከቤ ላይ ጌታዬ ተኝተህ ይሄ ሁሉ ሲሆን አታይም ወይ ነቅተህ የሚሆነው ሳይገባኝ ተጨንቄ ሳምጥ ታንኳዬ በውሃ ሲሞላ ስናወጥ ማዕበል የሚታዘዝህ የሚሰማህ ወጀቡ በተነሳህ ጊዜ ያወኩኝ ዝም አሉ ምንም ምንም አይሳንህም የማመልክህ ጌታ ትችላለህ ሁሉንም ኡ ባለመድሃኒት ያልተገኘላት አስራሁለት አመት ደም እየፈሰሳት ኡ ተንከራታች ያላትን ሁሉ አጥታ ማንም አልተገኘም ችግሯን የሚፈታ ከህዝብ ሁሉ መሀል በእምነት ተጋፍታ ፈውሷን ተቀበለች የልብሱን ጫፍ ነክታ ለስንቱ መለኛ ላዋቂ ያቃተ ድንቅ መካር ሃያል ቀላል ነው ለአንተ ምንም ምንም አይሳንህም የማመልክህ ጌታ ትችላለህ ሁሉንም ኸረ ምንም ምንም አይሳንህም የማመልክህ ጌታ ትችላለህ ሁሉንም ኸረ ምንም ምንም አይሳንህም