Yadeha Tetara
Yilma Hailu
4:43ፈያታዊ ዘየማን አምላኩን ለመነ በቀኝ ያቆመው ዘንድ ጌታን ተማጸነ ወንበዴ ብሆንም ሽፍታ ወንጀለኛ መምጣትህን አሰብኩ ለድህነት ወደኛ አልሰማሁም እኔ የነቢያትን ቃል አላወቅኩም በእርግጥ አብሮኝ እስኪሰቀል ኢሳይያስ ሲናገር ዳዊት ሲመሰክር የመሲሁን መምጣት አልሰማሁም ነበር አዝ በመስቀል ላይ ሳለ አምላኬን ለየሁት ትሁት ነበር ፍጹም በደል የሌለበት ስለ በደላችን እኛ ተሰቅለናል እሱ ግን በማን ላይ ወንጀልን ፈጽሟል አዝ ጨረቃ ደም ሆና ፀሐይዋ ስትጨልም ከዋክብት ረግፈው ሰማይ ሲያጉረመርም አምላክ መሰቀሉን ተፈጥሮ ነግራኝ ነው በመንግሥትህ ጌታ አስበኝ የምለው አዝ አወይ ቀያፋ ሆይ አወይ ሀና ሆይ ደስ ብሏችሁ ዋለ በጌታ ስቃይ ተፈጥሮ ምስክር ሆኖ ሲያስተምራችሁ እንዴት አላመነም ደንዳናው ልባችሁ