Elef Wede Mado
Azeb Hailu
አዝ፦ ለጌትነቱ ፡ ወሰን ፡ የለዉ ይህንን ፡ አምላክ ፡ ማን ፡ ልበለዉ በምንስ ፡ ቋንቋ ፡ ስለርሱ ፡ ላውራ ታምራቶቹን ፡ የፍቅሩን ፡ ሥራ (፪x) (አሃሃሃሃ) ፡ ከምድር ፡ ጫፍ ፡ እስከ ፡ ጫፍ (አሃሃሃሃ) ፡ እርሱን ፡ ያመልካሉ (አሃሃሃሃ) ፡ ትዕዛዙን ፡ ይሰማል (አሃሃሃሃ) ፡ ንፋስ ፡ ማዕበሉ የሰማይ ፡ ሠራዊት ፡ የሚያውጁለት በጐነቱንና ፡ የርሱን ፡ ጌትነት (፪x) አዝ፦ ለጌትነቱ ፡ ወሰን ፡ የለዉ ይህንን ፡ አምላክ ፡ ማን ፡ ልበለዉ በምንስ ፡ ቋንቋ ፡ ስለርሱ ፡ ላውራ ታምራቶቹን ፡ የፍቅሩን ፡ ሥራ (፪x) (አሃሃሃሃ) ፡ ክብርን ፡ እንዲያወሩ (አሃሃሃሃ) ፡ ያበጃጀሃቸው (አሃሃሃሃ) ፡ የሚያሞጋግሱህ (አሃሃሃሃ) ፡ እንዴት ፡ ብዙ ፡ ናቸው አእላፋት ፡ በሰማይ ፡ እልፎች ፡ በምድር ድንቅ ፡ ነህ ፡ ይሉሃል ፡ አንተን ፡ እግዚአብሔር አእላፋት ፡ በሰማይ ፡ እልፎች ፡ በምድር ጌታ ፡ ነህ ፡ ይሉሃል ፡ አንተን ፡ እግዚአብሔር አዝ፦ ለጌትነቱ ፡ ወሰን ፡ የለዉ ይህንን ፡ አምላክ ፡ ማን ፡ ልበለዉ በምንስ ፡ ቋንቋ ፡ ስለርሱ ፡ ላውራ ታምራቶቹን ፡ የፍቅሩን ፡ ሥራ (፪x) (አሃሃሃሃ) ፡ አፍ ፡ ያለው ፡ የሌለው (አሃሃሃሃ) ፡ መልእክት ፡ አለኝ ፡ ይላል (አሃሃሃሃ) ፡ የሰራኝ ፡ እግዚአብሔር (አሃሃሃሃ) ፡ ነው ፡ ብሎ ፡ ያወራል በግራና ፡ በቀኝ ፡ በሁሉም ፡ አቅጣጫ ፍጥረት ፡ የሚያወራው ፡ ያንተን ፡ ችሎት ፡ ብቻ በግራና ፡ በቀኝ ፡ በሁሉም ፡ አቅጣጫ ፍጥረት ፡ የሚያወራው ፡ ያንተን ፡ ስልጣን ፡ ብቻ አዝ፦ ለጌትነቱ ፡ ወሰን ፡ የለዉ ይህንን ፡ አምላክ ፡ ማን ፡ ልበለዉ በምንስ ፡ ቋንቋ ፡ ስለርሱ ፡ ላውራ ታምራቶቹን ፡ የፍቅሩን ፡ ሥራ (፪x)