Sinegam
Daniel Amdemichael
4:54ባባቴ ቤት ሁሉ ሞልቶ ተትረፍርፎ ኧረ ምን ጠፍቶ ከሱ ላይ አይኔ ተነሳ ላይጠቅመው ሌላውን አይቶ የእራሴ መንገድ አጠፋኝ ተጎዳሁኝ ሆ ከርያ ለመዋል ተገደድኩኝ ዛሬ ፍቅሩን ናፍቄያለሁ እመለሳለሁ ሆ እንደልጅ ባልሆን ባሪያ ሆናለው አዝ፦ ያለሱማ ኑሮ እንደማይሆን ተረዳሁ አሁን ይብቃኝ ምንም ላላተርፍ ተጎዳሁ ልመለስ የቀድሞ ቤቴ ይሻለኛል ሆ ከኢየሱስ ጋር ኑሮ ይመቸኛል የዓለም ኑሮ አንገፍግፎኛል ብዙ አራቅቶኛል ሆ ቸሩ አባቴ እርሱ ይሻለኛል መስሎኝ ነበር የተጠቀምኩ ድርሻዬን ይዤ ኮበለልኩ ሀብቴን በሜዳ በተንኩኝ አይ ሞኙ መች አስተዋልኩኝ ያባቴን ምክር ሳልሰማ በመቅረቴ ሆ ረሃብ ጎዳኝ ተጣብቆ አንጀቴ ልመለስ ፊቱን ለማየት ብዙም ባልደፍርም ሆ እንደ እግዚአብሔር ከቶ አይገኝም ገንዘብ አላፊ ጠፊ ነው ሰው ድጋፍ አይሆን ሸምበቆ ነው ልጅነቴ አታለለኝ አርቆ አለማሰቤ ጎዳኝ ዛሬስ የእግዚአብሔርን ምህረት ናፍቄያለሁ ሆ አይጨክንም ይኸን አውቃለሁ ጉስቁልናዬንም አይቶ ያዝንልኛል ሆ ውዱ አባቴ ይቅር ይለኛል አዝ፦ ያለሱማ ኑሮ እንደማይሆን ተረዳሁ አሁን ይብቃኝ ምንም ላላተርፍ ተጎዳሁ ልመለስ የቀድሞ ቤቴ ይሻለኛል ሆ ከኢየሱስ ጋር ኑሮ ይመቸኛል የዓለም ኑሮ አንገፍግፎኛል ብዙ አራቅቶኛል ሆ ቸሩ አባቴ እርሱ ይሻለኛል መድኔ ጋር እመለሳለው ሀዘኔን በዚያ ረሳለው ጉስቁልናዬም ይቀራል እግዚአብሔር ለኔ ይራራል ያደፈ ልብሴን አውልቆ ሌላ ያለብሰኛል ሆ ጌታ ፍቅሩን ይመግበኛል መንፈሱን ያፈስልኛል እፅናናለው ሆ ለዘላለም በርሱ አርፋለው