Diro Gena
Dawit Getachew Abreham
5:38ማዕበል ፡ ውስጥ ፡ ሆኖ ፡ ከአንተ ፡ ጋራ ፡ መሄድ ፡ ነው (፪x) በወጀብም ፡ መሃል ፡ ከአንተ ፡ ጋራ ፡ መሄድ ፡ ነው ፡ መሄድ ፡ ነው በባሕር ፡ ላይ ፡ ሆኖ ፡ ከአንተ ፡ ጋራ ፡ በሚያስፈራራው ተሽመድምዶ ፡ መቅረት ፡ ለምንድን ፡ ነው ፡ ግራ ፡ እንደገባው ከቶ ፡ ለምን ፡ ይሆን ፡ ከአንተ ፡ ጋራ ፡ የምንፈራው የዘወትር ፡ ልመና ፡ አሃሃሃ ፡ የምናደርሰው አዝ:- ጌታ ፡ ሆይ ፡ እባክህ ፡ ዓይኖቻችንን ፡ ክፈተው በእውነት ፡ ከእኛ ፡ ጋራ ፡ መሆንህን ፡ እንድናውቀው (፪x) አንተ ፡ እያለህ ፡ ሁሉን ፡ ቻይ ፡ ከጐናችን እንፈራለን ፡ ወጀብን ፡ እያየን እምነታችንም ፡ በሁኔታዎች ፡ ጥለን ወየሁ ፡ ጠፋን ፡ እያልን ፡ እንጮሃለን ከእንግዲህ ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ቀና ፡ ብለን ፡ እንሄዳለን ወጀቡን ፡ እንፈራውም ፡ በስምህ ፡ እንረግጠዋለን ለአእዋፍ ፡ ሁሉ ፡ የምታጠግብ ፡ ነህ ለእኛ ፡ ለልጆችህ ፡ እንዴት ፡ ትነሳለህ ብታደርግ ፡ ሁልጊዜ ፡ አሃ ፡ መች ፡ እናውቅሃለን ስለሚቀጥለው ፡ ደግሞ ፡ ብዙ ፡ እናስባለን ጌታ ፡ አንተን ፡ ብናይ ፡ አሃ ፡ ይህ ፡ ባልሆነ ፡ በእኛ እምነት ፡ ጨምርልን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምነው ፡ በ. (1) . አዝ:- ጌታ ፡ ሆይ ፡ እባክህ ፡ ዓይኖቻችንን ፡ ክፈተው በእውነት ፡ ከእኛ ፡ ጋራ ፡ መሆንህን ፡ እንድናውቀው (፪x) አንተ ፡ እያለህ ፡ ሁሉን ፡ ቻይ ፡ ከጐናችን እንፈራለን ፡ ወጀብን ፡ እያየን እምነታችንም ፡ በሁኔታዎች ፡ ጥለን ወየሁ ፡ ጠፋን ፡ እያልን ፡ እንጮሃለን ከእንግዲህ ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ቀና ፡ ብለን ፡ እንሄዳለን ወጀቡን ፡ እንፈራውም ፡ በስምህ ፡ እንረግጠዋለን አንፈራም ፡ ወጀቡን ፡ አንፈራም ፡ አንፈራም